ዑመር ቢን አልኸጧብ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- ከዕለታት አንድ ቀን ጂብሪል ዐለይሂ ሰላም በሶሐቦች መካከል አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና በማይታወቅ ሰው ተመስሎ እንደወጣ ይናገራሉ። ከዚህም ሰውዬ ባህሪ ልብሱ እጅግ የነጣ፣ ፀጉሩም እጅግ የጠቆረ ነበር። በሱ ላይም ድካም፣ አቧራ፣ የፀጉር መንጨባረርና የልብስ መቆሸሽ የመሰሉ የጉዞ ምልክት አይታይበትም። ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ዘንድ ተቀምጠው ከነበሩ ታዳሚዎች መካከልም አንድም ሰው አላወቀውም። ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ፊት እንደተማሪ አቀማመጥ ተቀመጠ። ስለ ኢስላምም ጠየቃቸው። እሳቸውም በሁለቱ የምስክር ቃላት ማረጋገጥን፣ አምስቱ ሶላቶች ላይ መጠባበቅን፣ ለሚገባው ሰው ዘካ መስጠትን፣ የረመዷን ወር መፆምን፣ በቻለ ላይ ግዴታ የሆነውን ሐጅ መፈፀምን ያካተተውን እነዚህን ማዕዘናት በመጥቀስ መለሱለት።
ጠያቂውም "እውነት አልክ!" አለ። ሶሐቦችም ከላይ ሲታይ አጠያየቁ አለማወቁን የሚጠቁም፤ ከዛ ደግሞ ትክክለኛ መልስ እንደተመለሰለት ማረጋገጡን በማስተዋላቸው ግራ ተጋቡ።
ከዚያም ስለ ኢማን ጠየቃቸው። እሳቸውም እነዚህን ስድስት ማዕዘናት ማመንን የሰበሰበ መልስ መለሱለት። እነሱም:-አላህ በመኖሩ፣ በባህሪያቶቹ፣ መፍጠርን በመሰሉ ድርጊቶቹና በአምልኮም ብቸኛ መሆኑን ማመን፤ አላህ ከብርሃን የፈጠራቸው መላእክቶች የተከበሩ ባሮቹ መሆናቸውን፣ አላህን የማያምፁና በትእዛዙ የሚተገብሩ መሆናቸውን ማመን፤ እንደ ቁርኣን፣ ተውራት፣ ኢንጂልና ሌሎችም ከአላህ ዘንድ በመልክተኞች ላይ በወረዱ መጽሐፍት ማመን፤ የአላህን ሃይማኖት የሚያደርሱ በሆኑ መልክተኞች ማመን ከነሱም መካከል ኑሕ፣ ኢብራሂም፣ ሙሳ፣ ዒሳና የመጨረሻቸው የሆኑት ሙሐመድ ሰለላሁ ዐለይሂም ወሰለምና ሌሎችም ነቢያቶችና መልክተኞች ይጠቀሳሉ። በመጨረሻው ቀን ማመን፤ እዚህ ምውስጥም ከሞት በኋላ ያሉ በቀብርና በበርዘኽ ህይወት እንዲሁም የሰው ልጅ ከሞት በኋላ የሚቀሰቀስና የሚተሳሰብ መመለሻውም ወይ ወደ ጀነት ወይ ወደ እሳት መሆኑን ማመንንም ያካትታል። አላህ በቀደመ ዕውቀቱ መሰረት፣ ጥበቡ ባስፈረደው መልኩ በፍላጎቱ መሰረት ነገሮችን እንደወሰነና በጽሑፍም እንዳሰፈረ ማመን፤ ምድር ላይ የሚከሰቱትም በወሰናትና በፈጠራት ልክ መሆኑንም ማመን ነው። ከዚያም ስለ ኢሕሳን (ስራን ማሳመር) ጠየቃቸው። ኢሕሳን ማለት ልክ አላህን እያዩ እንደሆነ እያሰቡ አላህን መገዛት ነው። እዚህ ደረጃ ላይ መድረስ ባይረጋገጥለት (ባይችል) እንኳ ልክ አላህ እርሱን እያየው እንደሆነ በማሰብ አላህን መገዛት ነው። የመጀመሪያው: የ "ሙሻሀዳህ" (አሏህን እያየህ እንደሆነ እያሰብክ የምታመልክበት) ደረጃ ነው እሱም የላቀ ደረጃ ነው። ሁለተኛው ደግሞ የ "ሙራቀባህ" (አሏህ እያየኝ ነው በሚል ሃሳብ የምታመልክበት) ደረጃ ነው።
ከዚያም ሰዓቲቱ መቼ እንደሆነች ጠየቃቸው። ነቢዩም ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም የሰዓቲቱ መከሰቻ ጊዜ አላህ በእውቀቱ ብቸኛ ከሆነበት ጉዳይ አንዱ በመሆኑ ተጠያቂውም ይሁን ጠያቂው ከፍጥረቱ መካከልም አንድም እንደማያውቀው ገለፁ።
ከዚያም ስለ ሰዓቲቱ ምልክቶች ጠየቃቸው። ከምልክቶቿ መካከል የጭን ገረዶችና ልጆቻቸው እንደሚበዙ ወይም የልጆች የእናቶቻቸውን ሐቅ አለመወጣታቸው እንደሚበዛ ይህም ከእናቶቻቸው ጋር ያላቸው መስተጋብር ልክ ከባሪያ ጋር እንዳላቸው አይነት መስተጋብር እንደሚሆን፤ ለበግ እረኞችና ለድሆች በመጨረሻው ዘመን ዱንያ ተዘርግታላቸው በህንፃ ውበትና አሰራር እንደሚፎካከሩ ገለፁ።
ከዚያም ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ጠያቂው ጂብሪል እንደነበረና የመጣውም ይህንኑ ቀጥተኛ እምነት ለሶሐቦች ሊያስተምር እንደሆነ ተናገሩ።
Hadeeth details